ሚያዝያ 16፣2016በአዲስ አበባ በአፈር እና ግንብ መናድ አደጋ ስድስት ሰዎች ሞቱ፡፡
- sheger1021fm
- Apr 24, 2024
- 1 min read
በአዲስ አበባ በአፈር እና ግንብ መናድ አደጋ ስድስት ሰዎች ሞቱ፡፡
አደጋው ያጋጠመው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጅድ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ሌሊት 11:00 ሰዓት ላይ ነው ተብሏል፡፡
የግለሰብ መኖሪያ ቤት አፈርና ግንብ ተንዶ በደረሰው በዚህ አደጋ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች በመኖሪያ ቤታቸው ተኝተው የነበሩ ናቸው ተብሏል።
በአደጋው ምክንያት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የደረሰውን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ወደፊት እናሳውቃለን ሲሉ የአዲስ አበባ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: @ShegerFMRadio102_1
Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio
Website: https://www.shegerfm.com/
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments