top of page

ሚያዝያ 16፣2016በአዲስ አበባ በአፈር እና ግንብ መናድ አደጋ ስድስት ሰዎች ሞቱ፡፡

  • sheger1021fm
  • Apr 24, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ በአፈር እና ግንብ መናድ አደጋ ስድስት ሰዎች ሞቱ፡፡


አደጋው ያጋጠመው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጅድ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ሌሊት 11:00 ሰዓት ላይ ነው ተብሏል፡፡

የግለሰብ መኖሪያ ቤት አፈርና ግንብ ተንዶ በደረሰው በዚህ አደጋ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች በመኖሪያ ቤታቸው ተኝተው የነበሩ ናቸው ተብሏል።


በአደጋው ምክንያት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የደረሰውን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ወደፊት እናሳውቃለን ሲሉ የአዲስ አበባ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል።


ንጋቱ ረጋሳ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: @ShegerFMRadio102_1




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page