top of page

ሚያዝያ 1 2017 - የኤሌክትሪክ አገልግሎት ካለፉት 3 ቀናት ጀምሮ በሲስተም መቋረጥ ምክንያት ደንበኞች ሒሳብ እየከፈሉን አይደለም አለ

  • sheger1021fm
  • Apr 9
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ካለፉት ሶሰት ቀናት ጀምሮ በሲስተም መቋረጥ ምክንያት ደንበኞች ሒሳብ እየከፈሉን አይደለም አለ፡፡


ቴክኒካል ያለውን ችግር ለመፍታት እየሰራ መሆኑን የተናገረው አገልግሎቱ የመክፈያ የጊዜው ገደቡ ቢያልፍ እንኳን የደንበኞችን አገልግሎት አናቋርጥም ወይም ቆጣሪ አንቆርጥም ሲል ተናግሯል፡፡

አገልግሎቱ በባንክ ሒሳብ የሚከፈልበት ሲስተም ብቻ ሳይሆን የክፍያ መረጃን ጨምሮ ቅሬታ ፣ ጥቆማና ጥያቄዎችን የሚቀበልበት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎችም እንደማይሰሩ ተነግሯል፡፡


ተቋሙ ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ ጠይቆ በተቻለ ፍጥነት ሲስተሙ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት እና አገልግሎት ለማስጀመር እየሰራሁ በመሆኑ በትዕግስት ጠብቁን ብላችኋል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Kommentit


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page