top of page

መጋቢት 6፣2016 - አየር መንገዱ ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ለነበረው ምስል ምላሽ ሰጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ የአየር መንገዱን ዩኒፎርም የለበሰ ሰራተኛን የራሱን ሻንጣ በማስተካከል ላይ ሳለ የሚያሳይ ምስል ከተሳሳተ መረጃ ጋር በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመዘዋወር ላይ እንዳለ ተመልክቻለሁ ብሏል።


በማህበራዊ ሚዲያ በተዘዋወረው ምስል ላይ የሚታየው ግለሰብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ባልደረባ ሲሆን የአየር መንገዱ ዓርማ የታተመበት ሻንጣም የሰራተኛው መሆኑን አየር መንገዱ አስረድቷል።


እንዲሁም በምስሉ ላይ የሚታየው ቦታ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ባልደረቦቻችን የግል ንብረቶቻቸውን እና ለስራ የሚገለገሉባቸውን ቁሳቁሶች የሚያስተካክሉበት አካባቢ መሆኑን እና ሌሎቹ ቦርሳዎችም በምስሉ ላይ ያልተካተቱ የሌሎች ባልደረቦቻችን ቦርሳዎች እንደሆኑ ጠቅሷል።


በተጨማሪም ስፍራው የመንገደኞች ሻንጣ ሊገኝበት የማይችል ለሰራተኞቻችን ብቻ የተከለለ ቦታ ከመሆኑም በተጨማሪም ሳምንቱን ሙሉ ለ24 ሰዓት በደህንነት የካሜራ ዕይታ ውስጥ የሚገኝ ነው ብሏል።


በስራ ገበታው ላይ የሚገኝ የአየር መንገዱ ሰራተኛን ተግባር ህገወጥ አስመስሎ ለማቅረብ መሞከሩ እንዳሳዘነውም በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስፍሯል።



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page