top of page

መጋቢት 30 2017 - በ5 ተፋሰሶች በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለሚተግበር ታቅዶ የነበረው የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ ዛሬ በሶስቱ ወንዞች ላይ ተጀምሯል

  • sheger1021fm
  • Apr 8, 2025
  • 1 min read

በ5 ተፋሰሶች በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለሚተግበር ታቅዶ የነበረው የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ ዛሬ በሶስቱ ወንዞች ላይ ተጀምሯል፡፡


በተከዜ፣ አባይ፣ አዋሽ፣ ኦሞ ጊቤ፣ ሪፍት ቫሊ ተፋሰሶች ላይ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለመጀመር ታቅዶ ነበር ነገር ግን ዛሬ በአዋሽ ፣ በአባይ እና በተከዜ ተፋሰሶች ላይ የውሃ ሀብት አስተዳደር የማስጀመር ስራ ተካሂዷል፡፡


ፕሮጀክቱ በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በውሃ እና መሬት ማዕከል ይተገበራል የተባለ ሲሆን የገንዘብ ድጋፉ ከኔዘርላንድ ኤምባሲና ከአውሮፓ ህብረት የተገኘ ነው ተብሏል፡፡


ፕሮጀክቱ በውሃ ምክንያት የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወደ ወንዞች የሚለቀቁ በካዮችን እና ፍሳሽ ቆሻሻዎችን ለመከላከል እና የውሃ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ይረዳል ተብሏል፡፡


ፕሮጀክቱ በ5 ዓመት ውስጥ ይከናወናል የተባለ ሲሆን በአስራ አንድ ክልሎች 74 ዞኖች እና 724 ወረዳዎችን እንደሚያካልል ተነግሯል፡፡


የተፋሰስ አስተዳደር ድጋፍ ለጠንካራ ፣ አካታችና ተስማሚ ለውጥ ለኢትዮፕያ ብሔራዊ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም ይሰኛል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page