top of page

መጋቢት 30 2017 - በ5 ተፋሰሶች በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለሚተግበር ታቅዶ የነበረው የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ ዛሬ በሶስቱ ወንዞች ላይ ተጀምሯል

  • Apr 8, 2025
  • 1 min read

በ5 ተፋሰሶች በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለሚተግበር ታቅዶ የነበረው የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ ዛሬ በሶስቱ ወንዞች ላይ ተጀምሯል፡፡


በተከዜ፣ አባይ፣ አዋሽ፣ ኦሞ ጊቤ፣ ሪፍት ቫሊ ተፋሰሶች ላይ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ በ45 ሚሊዮን ዩሮ ለመጀመር ታቅዶ ነበር ነገር ግን ዛሬ በአዋሽ ፣ በአባይ እና በተከዜ ተፋሰሶች ላይ የውሃ ሀብት አስተዳደር የማስጀመር ስራ ተካሂዷል፡፡


ፕሮጀክቱ በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በውሃ እና መሬት ማዕከል ይተገበራል የተባለ ሲሆን የገንዘብ ድጋፉ ከኔዘርላንድ ኤምባሲና ከአውሮፓ ህብረት የተገኘ ነው ተብሏል፡፡


ፕሮጀክቱ በውሃ ምክንያት የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ወደ ወንዞች የሚለቀቁ በካዮችን እና ፍሳሽ ቆሻሻዎችን ለመከላከል እና የውሃ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ይረዳል ተብሏል፡፡


ፕሮጀክቱ በ5 ዓመት ውስጥ ይከናወናል የተባለ ሲሆን በአስራ አንድ ክልሎች 74 ዞኖች እና 724 ወረዳዎችን እንደሚያካልል ተነግሯል፡፡


የተፋሰስ አስተዳደር ድጋፍ ለጠንካራ ፣ አካታችና ተስማሚ ለውጥ ለኢትዮፕያ ብሔራዊ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም ይሰኛል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page