top of page

መጋቢት 27፣2016 - የገንዘብ ተቋማት ለፈጠራ ውጤቶችም ብድር በማቅረብ ዘርፉን ማገዝ አለባቸው ተባለ

  • sheger1021fm
  • Apr 5, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ከተለመደውና ዋስትናን መሠረት ካደረገ የብድር አገልግሎት ውጪ ባሉ አማራጮች ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።


በውይይቱ ላይ ሲነገር እንደሠማነው ለግል የፈጠራ ውጤቶች፣ ለባለቤትነት መብት ወይም ኮፒ ራይት፣ ለንግድ ምልክቶች እና ለንግድ ሚስጥሮች ብድር የማቅረብ አሰራር በኢትዮጵያ ሊለመድ ይገባል።


ለአዕምሯዊ ፈጠራ ውጤቶች የሚሰጥ ብድር የስራ ዕድል እንዲሰፋ ያግዛል ነው የተባለው።


የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የገንዘብ ችግር የሚያቃልል ሁነኛ መፍትሔ እንደሆነም ተጠቅሷል።


ለተጨማሪ ፈጠራ ሰዎችን እንደሚያነሳሳም የውይይቱ አዘጋጅ የሆነው የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምክትል ፀሃፊ አቶ ስዩም ጫኔ ተናግረዋል።


ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





ShegerFM: @ShegerFMRadio102_1

Комментарии


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page