top of page

መጋቢት 25፣2016 - አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ፕሮግራም ለማገዝ የሚያስችል ውይይት ማድረጉን ተናገረ

አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ፕሮግራም ለማገዝ የሚያስችል ውይይት ማድረጉን ተናገረ፡፡


የድርጀቱ ባልደረቦች በኢትዮጵያ ለ13 ቀናት ያደረጉትን ጉብኝት ማጠናቀቃቸው ተሰምቷል፡፡


በአልቫሮ ፕሪስ የተመራው የአለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አባላት የጉብኝታቸው አላማ IMF የኢትዮያን የኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራም በሚደግፉበት ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነበር ተብሏል፡፡


ከጉብኝቱ መጠናቀቅ በኋላ አጭር መግለጫ ያወጣው IMF የተደረገው ውይይት ከዚህ በፊት የተደረጉ ውይይቶች ተከታይ እንዲሆን አስረድቷል፡፡


በዚህም IMF እንዴት ባለ ሁኔታ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መደገፍ ይችላል በሚለው ላይ ተጠቃሚ ለውጥ የታየበት ምክክር ተደርጓል ብሏል፡፡


ይህ በውይይቱ ወቅት ታይቷል ስለተባለው ጠቃሚ ለውጥ ግን ድርጅቱ ያለው ነገር የለም፡፡


የኢትዮጵያ መንግስትም በጉዳዩ ላይ ያወጣው መግለጫ አልታይም፡፡


ውይይቱ በ IMF እና የአለም ባንክ የፀደይ ወቅት ምክክር ወቅትም ይቀጥላል ተብሏል፡፡


ንጋቱ ሙሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




ShegerFM: @ShegerFMRadio102_1

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page