top of page

መጋቢት 19፣2016 - በሚቀጥሉት 3 ዓመታት የ5 የሰብል አይነቶችን ምርጥ ዘር ለማብዛት እየተሰራ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 3 ዓመታት የ5 የሰብል አይነቶችን ምርጥ ዘር ለማብዛት እየተሰራ ነው ተባለ፡፡


ይህም የሆነው በሀገሪቱ የሚታየው የዘር እጥረት ስርጭትን ለመፍታት ነው የተባለ ሲሆን በየአመቱ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል ምርጥ ዘር ለመሰብሰብ ውጥን ተይዟል፡፡


የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) እንዳሉት ‘’ትኩረት የተሰጣቸው የሰብል አይነቶች ስንዴ በቆሎ ገብስ ጤፍ እና ማሽላ’’ ናቸው፡፡


እነዚህ ሰብሎች የሀገሪቱን 87 ከመቶ የምግብ ፍላጎት ይሸፍናሉ የተባለ ሲሆን ሀገሪቱ እየሰራች ላለችው የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የምርጥ ዘር ፍላጎቱ ሟሟላት ቅድሚያ የሚሰጠው ነው ተብሏል፡፡


ሚኒስትሩ እንዳሉት ከነዚህ ውጪ ያሉ የሰብል አይነቶች የዘር አቅርቦትና ብዜት ስራዎች ጎን ለጎን እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page