top of page

መጋቢት 18 2017 - ‘’ውል ላልያዙ እና ውላቸው ለተቋረጠ ሰራተኞች በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ከፍሏል’’ የተባለው ተቋም

  • sheger1021fm
  • Mar 27
  • 1 min read

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያላግባብ ወጪ ያደረገውን በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር እና ሌሎች በኦዲት ምርመራ የተገኙ የአሰራር ግድፈቶችን አስተካክሎ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለፓርላማው እንዲያሳውቅ ታዘዘ፡፡


ሚኒስቴር መ/ቤቱ በፕሮጀክትና ውል ላልያዙ እንዲሁም ውላቸው ለተቋረጡ #ሰራተኞች በሚሊዮን የሚቆጠር ብር መክፈሉም ተረጋግጧል ተብሏል፡፡


በኦዲት ምርመራ ከተረጋገጡት መካከል ጥቂቶቹ

- በድምሩ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ያላግባብ ወጭ ተደርጓል፡፡


- በውሉ መሰረት 493 ሺህ ብር መከፈል ላለበት አገልግሎት 4.4 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል፡፡


- ውል ለሌላቸው እና ውላቸው ለተቋረጡ ሰራተኞች በድምሩ ወደ 2 ሚሊዮን ብር የተጠጋ ብር ተከፍሏል፡፡


- የሚከወኑ ፕሮጀክቶች የቅድሚያ አዋጭነት ጥናት አይካሄድም፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….




ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r

Comments

Couldn’t Load Comments
It looks like there was a technical problem. Try reconnecting or refreshing the page.
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page