top of page

መጋቢት 18፣2016 - የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ አገራት በሚያስገባቸው የግብርና ምርቶች ላይ የጥራት ቁጥጥሩን እያጠበቀ ነው ተባለ።

  • sheger1021fm
  • Mar 27, 2024
  • 1 min read

የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ አገራት በሚያስገባቸው የግብርና ምርቶች ላይ የጥራት ቁጥጥሩን እያጠበቀ ነው ተባለ።


የህብረቱን የጥራት መስፈርት ለማሟላት ኢትዮጵያውያን ላኪ ነጋዴዎች ብዙ መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተነግሯል።


ኢትዮጵያውን ነጋዴዎች ቡና እና ሰሊጥን ጨምሮ በርከት ያሉ የግብርና ምርቶችን ወደ አውሮፓ ህብረት አባል አገራት ይልካሉ።


በተለይ ህብረቱ ከጦር መሳሪያ በስተቀር ሁሉም ምርቶች ወደ ገበያው እንዲገቡ የሰጠው ዕድል ኢትዮጵያውን ላኪዎችን በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ አድርጓል ተብሏል፡፡



ከዚሁ ጎን ጎን ህብረቱ በሚቀበላቸው ምርቶች ላይ የጥራት ቁጥጥሩን እያጠበቀ እንደሚገኝ ተሠምቷል።


ኢትዮጵያውን ላኪዎችም ይህንኑ አውቀው መስራት እንዳለባቸው የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ምክትል ፀሃፊ አቶ ስዩም ጫኔ ተናግረዋል።


ህብረቱ ሊተገብረው ያሰበው የጥራት ህግ የምርቱን መነሻ ፤ የማጓጓዝ ሂደት እና የማከማቻ ስርአት የሚፈትሽ እንደሆነ አቶ ስዩም ተናግረዋል ።


ህብረቱ እነዚህ አስገዳጅ የጥራት መስፈርቶች በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ስራ ላይ ያውላቸዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው የሰማነው።

 
 
 

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page