top of page

መጋቢት 13፣2016 - ''በንግድ ባንክ ላይ የተፈጠረዉ ክስተት የሳይበር ጥቃት አለመሆኑን አረጋግጫለሁ'' የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

  • Mar 22, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተፈጠረዉ ክስተት የሳይበር ጥቃት አለመሆኑን አረጋግጫለሁ ሲል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ተናገረ።

 

ያጋጠመው ከሲስተም ማሻሻያ ትግበራ ጋር በተያያዘ የተፈጠረ እንጂ የሳይበር ጥቃት መሆኑን የሚያሳይ መረጃ አለመገኘቱን  አስተዳደሩ ጋዜጠኞችን ጠርቶ ተናግሯል።

 

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ መስሪያ  ቤታቸው ባደረገዉ ምርመራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከውስጥም ይሁን ከውጭ ለሚቃጡበት የሳይበር ጥቃቶች አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል አቅም እንዳለዉና አስፈላጊውን የሳይበር ደህንነት ጥንቃቄ እንደሚያደርግ በባንኩ ሲስተሞች ላይ የተደረገዉ ፍተሻ እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

 

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባደረገው የደህንነት ፍተሻና ምርምራ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተፈጠረዉ የሲስተም ችግር የሳይበር ጥቃት ምክንያት መሆኑን የሚያሳይ ምንም ዓይነት መረጃ አለመገኘቱን ወ/ሮ ትዕግስት አስረድተዋል።

 

ነገር ግን ችግሩ እንዲከሰት ምክንያት የሆኑ ጉዳዮች በምርመራ የትለዩ ሲሆን ይህም ባንኩ በሞባይል ሲስተሙ ላይ ባደረገዉ የማሻሻያ ሥራ የተከሰተ መሆኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።

 

 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ማሻሻያ በሚደረግበት ወቅት ቀደም ብሎ ሌላ ሲስተም ማለትም T24 (ኮር ባንኪንግ ሲስተም) ጥቅም ላይ የዋለ የስሌት ሞጁል ወይም አልጎሪዝም በመውሰድ በሞባይል ባንኪንግ ሲስተሙ ላይ በቀጥታ ለመተግበር በተረገ ሙከራ ችግሩ መከሰቱን  ሲነገር ሰምተናል።

 

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባደረገው ምርመራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲስተም ጃር ፋይል ሶርስ ኮድ (JAR Files Source Code) ወስዶ ባደረገዉ ምርመራና ትንተና የፕሮግራሚንግ ቅደም ተከተሉ ወይም ሎጂካል ፍሰቱ የተዛባ ሆኖ በመገኘቱ ነው ተብሏል፡፡

 

አስተዳደሩ ተጨማሪ ምርመራዎች እና የፎረንሲክ ስራዎችን በማከናወን ውጤቱን ለሕብረተሰቡ ይፋ እንደሚደረግም የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ተናግረዋል።

 

 

ፍቅሩ አምባቸው


 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page