top of page

መጋቢት 12 2017 - ከተቀጣሪው ደመወዝ ላይ መንግስት ለአደጋ ጊዜ ፈንድ በሚል በየወሩ ገንዘብ መቁረጥ ሊጀምር ነው

  • sheger1021fm
  • Mar 21
  • 1 min read

ከተቀጣሪው #ደመወዝ ላይ መንግስት ለአደጋ ጊዜ ፈንድ በሚል በየወሩ ገንዘብ መቁረጥ ሊጀምር ነው፡፡


የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር አዋጅ ለሚደርሱ የተለያዩ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት እንደሚሰራ ደንግጓል፡፡


ለዚህም ደመወዝተኞች በየወሩ ከደመወዛቸው እንዲያዋጡ እንዲሁም የንግድ ፈቃድ ሲያወጡም ሆነ ሲያድሱ በቁርጥ ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚስገድድ ነው፡፡


ደመወዝተኛው እስካሁን እስከ 35 በመቶ የገቢ ግብር፣ 7 በመቶ የጡረታ በድምሩ 42 በመቶ ድረስ በየወሩ ሲቆረጥበት ቆይቷል፡፡


ይቋቋማል ለተባለው የአደጋ ፈንድ ምን ያህል በመቶ እንዲቆረጥ ግን እስካሁን አልታወቀም፡፡


ተቋማትም መዋጮ እንዲያደርጉ የሚገደዱ ይሆናል የተባለ ሲሆን ምን ያህል በመቶ ያዋጣሉ ለሚለው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዝርዝር ደንብ ይወጣል ተብሏል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…




ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page