top of page

መጋቢት 11 2017 - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትግራይ ክልል ባለው ጊዜአዊ አስተዳደር ውስጥ በግለሰብ ደረጃ የስልጣን ልውውጥ ሊኖር እንደሚችል ተናገሩ

  • sheger1021fm
  • Mar 20
  • 1 min read

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትግራይ ክልል ባለው ጊዜአዊ አስተዳደር ውስጥ በግለሰብ ደረጃ የስልጣን ልውውጥ ሊኖር እንደሚችል ተናገሩ፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግለሰቦች ደረጃ በጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የስልጣን ለውጥ ሊኖር እንደሚችል በዛሬው የፓርላማ ቆይታቸው ተናግረዋል፡፡


በጊዜአዊ አስተዳደሩ ላለፉት 2 ዓመታት ለሰራው ስራ አድናቆት የቸሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የጊዜአዊ አስተዳደሩ የሁለት ዓመት የስልጣን ቆይታ አሁን አብቅቷል ብለዋል፡፡


በዚህም ምክንያት #የህግ_ማሻሻያ የሚፈልግ ጉዳይ አለ፤ ተጨማሪ ጊዜ ስለሚፈልግ መሻሻል አለበት ህጉ ሲሻሻል ደግሞ የነበረው አፈፃፀም መገምገም አለበት፡፡

ተገምግሞም መጠነኛ ለውጥ ተደርጎ የፕሪቶሪያው ስምምነት ባከበረ መንገድ ጊዜአዊ አስተዳደሩ የሚቀጥለው ምርጫ ድረስ ስራውን እየሰራ ህዝቡን ለምርጫ ለማዘጋጀት መስራት አለበት ብለዋል፡፡


ይህ ለማድረግ ከክልሉ ጊዜአዊ አስተዳደር ፕሬዘዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና ከምክትሎቻቸው ጋር ውይይት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህውሃትን ጨምሮ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋርም ውይይት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡


በዚህ ንግግር መሰረት ህግ አሻሽለን ለሚቀጥለው አንድ ዓመት ጊዜአዊ አስተዳደሩ ይቀጥላል የሚል እምነት አለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጊዜአዊ አስተዳደሩ ሲቀጥል ደግሞ በግለሰቦች ደረጃ የስልጣን ለውጥ ሊኖር ይችላል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page