top of page

መጋቢት 10 2017 - በአዲስ አበባ ንግድ ቤቶችና ትራንስፖርት ሰጭዎች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ምሽት ሶስት ተኩል እና አራት ሰዓት አገልግሎት መስጠት አለባቸው ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Mar 19
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ንግድ ቤቶች እና ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ምሽት ሶስት ተኩል እና አራት ሰዓት አገልግሎት መስጠት አለባቸው ተባለ፡፡


በከተማዋ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው አካባቢዎች ሱቆች እና ሌላም የንግድ አገልግሎት ሰጭዎች እስከ ምሽት በራቸውን እንዳይዘጉ ወይም በራቸው ዝግ ከሆነ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት በራቸው ላይ እንዲያኖሩ የሚያስገድደው ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ ገብቷል ተብሏል፡፡


ይህን ያለው የከተማዋ ንግድ ቢሮ ነው፡፡

በመንገድ ዳር ያሉ #ንግድ_ቤቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እስከ ሶስት ሰዓት ተኩል የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ደግሞ እስከ 4 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ደንቡ ያስገድዳል፡፡


ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎችም እስከ ምሽት 4 ሰዓት ሲቆዩ ከተፈቀደው ታሪፍ በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ በደንቡ ተደንግጓል፡፡


ይህም ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page