top of page

መጋቢት 10፣2016 - የኦሮሚያ ክልል ምርቶች  ወደ አዲስ አበባ  እንዳይገቡ መሰናክል ሆኗል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት እየሰራሁ ነው  ብሏል

የኦሮሚያ ክልል የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች በበቂ መጠን ወደ አዲስ አበባ  እንዳይገቡ መሰናክል ሆኗል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት እየሰራሁ ነው  ብሏል።

 

 በአዲስ አበባ የአንዳንድ አትክልቶች ዋጋ ከሠሞኑ ቅናሽ አሳይቷል፤ ለዚህ አንዱ ምክንያት አጎራባች ከሆነው የኦሮሚያ ክልል ምርቶቹ በስፋት ወደ ከተማ እንዲገቡ መደረጉ ነው ተብሏል፡

 

የኦሮሚያንግድ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ጌሾ ለሸገር እንዳሉት በውሃ እና መሰል ምክንያቶች ቀንሶ የነበረው ምርት አሁን በተሻለ መጠን ወደ ከተማዋ እየገባ ነው ብለውናል።

 

በኦሮሚያክልል የሚታው የፀጥታ ችግርም አትክልትና ፍራፍሬ በበቂ መጠን ወደ አዲስ አበባ ገብቶ ለተጠቃሚው እንዳይቀርብ ምክንያት መሆኑ ይነሳል።

 

ይሄ የፀጥታ ችግርስ ምን ያህል ተሻሽሏል.ያልናቸው የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተውናል።

 

በክልሉ.የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራትን በአዲስ አበባ ከተማ ካሉት ጋር በማስተሳሰርም፤ የምርት አቅርቦቱ እንዲጨምር እያደረግን ነው ሲሉ አቶ ተስፋዬ ነግረውናል።

 

 

ንጋቱ ረጋሳ

 


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page