top of page

መስከረም 8፣2017 - 15 አለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች እስራኤል በጋዛ የተኩስ አቁም እንድታደርግ ጫና እንዲደረግባት ጠየቁ

15 አለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች እስራኤል በጋዛ የተኩስ አቁም እንድታደርግ ጫና እንዲደረግባት ጠየቁ፡፡


በእስራኤል ላይ አለም አቀፍ ጫና እንዲበረታባት ከጠየቁት አለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች መካከል ኦክስፋም፣ ሴቭ ዘ ቺልድረን እና ክርስቲያን ኤድ የተወሰኑት እንደሆኑ ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡


የረድኤት ድርጅቶቹ የጋዛውን ጦርነት ለማስቆም በእስራኤል ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብም እንዲደረግባት ጠይቀዋል፡፡


በአሁኑ ወቅት በጦርነቱ ምክንያት ወደ ጋዛ መድረስ የነበረበት 85 በመቶ እርዳታ መስተጓጎሉ ተጠቅሷል፡፡


ከጦርነቱ በፊት በየቀኑ 500 የጭነት መኪና እርዳታ ሲገባ ቆይቷል፡፡


በአሁኑ ወቅት ግን በየእለቱ የሚገባው ሰብአዊ እርዳታ ከ69 የጭነት መኪና አይበልጥም ተብሏል፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page