top of page

መስከረም 6፣2017 - የግብርና ሚኒስቴር በተጠናቀቀው 2016 ዓ.ም እሰራዋለሁ ካለው ጉዳይ አንዱ አሲዳማ መሬትን ማከም ነበር

  • Sep 16, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ከምታርሰው መሬት ውስጥ 43 ከመቶ ወይም 7 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው መሬቷ በአሲድ እንደተጠቃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተናግሮ ነበር፡፡


ከዚህ ውስጥ 3.1 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቂ አፈር ነው፡፡


መሬቱን ለግብርና ስራ ለማዋል በዓመት 6.2 ሚልየን ኩንታል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን መሬቱ አሲዳማ በመሆኑና በአግባቡ ስለማይቀበለው 70 ከመቶ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ይባክናል ተብሏል።


በዚህም ሀገሪቱ 19 ቢሊዮን ብር በአፈር አሲድ ምክንያት በዓመት ይባክንባታል ሲል የግብርና ሚኒስቴር ተናግሯል።


የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ በ #አሲዳማ_አፈር ምክንያት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ምርት ይባክንባታል ሲሉም አስረድተዋል።


አሲዳማ አፈር በአብዛኛው የሚከሰተው በደጋ እና ወይና ደጋ የኢትዮጵያ ክፍል አካባቢ ነው ያሉት ሚንስትሩ ለዚህም ምክንያቱ መሬቱ፤ በዝናብ ስለሚታጠብና በአንዳንድ የአፈር ማዳበርያ አጠቃቀም ተብሏል፡፡

አሲዳማ አፈር ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል የሚሉት ያለው የግብርና ሚንስቴር ይህንን ከወዲሁ ለማከም ኖራ እየተጠቀመ ይገኛል።


በዚህ ምክንት #የግብርና_ሚኒስቴር በክረምት ወቅት የመህር እርሻው ሲካሄድ ጎን ለጎን ቢያንስ 50,000 ሄክታር መሬት ሰርቶ ማሳያ አሲዳማ መሬትን ለማከም እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነበር፡፡


ይህንን በተመለከተ ከምን ደረሰ ብለን በግብርና ሚኒስቴር በተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ የአፈር ሀብት ልማት ስራ አስፈፃሚውን አቶ ሊሬ አብዩን ጠይቀናቸዋል፡፡


አቶ ሊሬ በዚህ ወቅት ለመስራት ከታቀደው የአሲዳማ አፈር የማከም ስራ የተሳካው 15,000 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ብቻ ነው ብለዋል፡፡


ለምን የታቀደው እቅድ አልተሳካም ብለን አቶ ሊሬን ጠይቀናቸዋል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታረሰው መሬት ከአሲዳማነት ባለፈ ሌሎችም ምርትና ምርታማነት እንዲቀንስ የሚያደርጉ እንደ ጨዋማ መሬትና ሌሎች በግብርናው ዘርፍ አሁን ላይ ያሉ ችግሮች እንደሚስተዋል ያስረዳሉ፡፡


አሁን ማሳካት ያልተቻለው አሲዳማ አፈር የማከም ስራ በ2017 ላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያዎች በአማራጭነት በመጠቀም እቅዱን ለማካካስና የበለጠ ለመስራት ውጥን አለን ሲሉ አቶ ሊሬ ያስረዳሉ፡፡


በበጋ ወቅት በሚካሄዱ የግብርና ስራዎች ጎን ለጎን የግብርና ኖራ ምርት እንዲጨምር በማድረግ ከአሁን በተሻለ መንገድ በመስራት አሲዳማ አፈር ማከም አለብን ይህ ከሆነ ምርትና ምርታማነት ያድጋል ሲሉ ነግረውናል፡፡



በረከት አካሉ

Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page