top of page

መስከረም 4፣2017 - ‘’የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ብቻውን የትምህርት ጥራቱን አይመልሰውም’’ ባለሞያዎች

  • sheger1021fm
  • Sep 14, 2024
  • 1 min read

ከሰሞኑ ይፋ ለተደረገው የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ከአምናውና ከካቻአምናው የተሻለ ቁጥር ያላቸው 5.4 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡


ከ95 በመቶ በላይ ተማሪዎች የመውደቃቸው ነገር የትምህርት ጥራቱ ያለውን ስር የሰደደ የጥራት ችግር ማሳያ ተደርጎ ይጠቀሳል፡፡


የትምህርት ባለሞያዎች በነበረው አሰራር ከቀጠልን ችግሩን መፍታት አንችልም ይላሉ፡፡


የት/ቤት ቁጥር መጨመር እና ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ የት/ት ሥርዓቱን መቀየር ብቻውን የትምህርት ጥራቱን ችግር ስለማይፈታው ተያያዥ መፍትሄዎችን አብሮ ማጤን ያስፈልጋል እያሉ ነው፡፡



ፋሲካ ሙሉወርቅ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page