top of page

መስከረም 30፣2017 - ህሙማን የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ መንግስት ጤና ተቋማት ሲሄድ ስድብን ጭምሮ የተለያ ውክቢያዎች እንደሚደርስባቸው ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 10, 2024
  • 1 min read

ህሙማን የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ መንግስት ጤና ተቋማት ሲሄድ ስድብን ጭምሮ የተለያ ውክቢያዎች እንደሚደርስባቸው ተነገረ፡፡


ይህ የተነገረው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ላይ ባደረገው ወይይት ነው፡፡


የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ህሙማንን ከእንግልት እና ከማመነጫጨቅ የሚጠብቅ እንዲሆን ተጠይቋል፡፡


ነዋሪዎች የህክምና እርዳታ ለማግኘት ወደ መንግስት የጤና ተቋማት ሲሄዱ ክብራቸውን በጠበቀ መንገድ እንዲስተናገዱ የእንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ጠይቀዋል፡፡


የጤና ተቋማት ህክምና እርዳት ሲሰጡ የታካሚውን ክብር እንዲጠብቁ በአዋጅ ሊካተት ይገባል ሲሉ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቶ አስቻለ አላምሬ ተናግረዋል፡፡


የጤና አገልግሎት የስነምግባር መርሆች ላይም ቅንነት እና ታማኝነት በረቂቅ አዋጁ እንዲካተት ተጠይቋል፡፡

ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page