ህሙማን የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ መንግስት ጤና ተቋማት ሲሄድ ስድብን ጭምሮ የተለያ ውክቢያዎች እንደሚደርስባቸው ተነገረ፡፡
ይህ የተነገረው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ላይ ባደረገው ወይይት ነው፡፡
የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ህሙማንን ከእንግልት እና ከማመነጫጨቅ የሚጠብቅ እንዲሆን ተጠይቋል፡፡
ነዋሪዎች የህክምና እርዳታ ለማግኘት ወደ መንግስት የጤና ተቋማት ሲሄዱ ክብራቸውን በጠበቀ መንገድ እንዲስተናገዱ የእንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ጠይቀዋል፡፡
የጤና ተቋማት ህክምና እርዳት ሲሰጡ የታካሚውን ክብር እንዲጠብቁ በአዋጅ ሊካተት ይገባል ሲሉ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቶ አስቻለ አላምሬ ተናግረዋል፡፡
የጤና አገልግሎት የስነምግባር መርሆች ላይም ቅንነት እና ታማኝነት በረቂቅ አዋጁ እንዲካተት ተጠይቋል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
댓글