top of page

መስከረም 28፣2017 - በ2017 በጀት ዓመት 700,000 ሰዎች ወደ ውጪ ሀገራት ለስራ ይላካሉ ተባለ

በ2017 በጀት ዓመት 700,000 ሰዎች ወደ ውጪ ሀገራት ለስራ ይላካሉ ተባለ፡፡


ይህንን ያሉት በትናንትነው ዕለት የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ናቸው፡፡


በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ለ4.3 ሚሊዮን ሰዎች የስራ እድል ለመፍጠር መታቀዱን ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል፡፡

ከእነዚህ መካካልም 700,000ዎቹ በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት የሚሰማሩ እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡


በዚህ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ላይም ጥራት እና ቁጥርሩ እንዲያድግ እንዲሁም በስራ ገበያ የመረጃ አስተዳደር ላይ ይሰራል ብለዋል፡፡


ለዚህም ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በጋራ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡


ኢትዮጵያ፤ በተለያዩ የስራ መስኮች ሰራተኞችን ወደተለያዩ ሀገራት እየላከች መሆኑን የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ተደጋግሞ ሲነገር ይሰማል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page