top of page

መስከረም 27 2018 - ‘’ሰዎችን አለመስማት፣ ለሰዎች ቅን መሆን አለመቻል፣ በስራ እና በትምህርት ውጤታማ አለመሆን የመቀንጨር ችግር ካለባቸው ሰዎች ጥቂቶቹ ምልክቶች ናቸው’’ ሀብቴ ጀቤሳ(ዶ/ር)

  • sheger1021fm
  • Oct 7
  • 1 min read

በመቀንጭር እና ተያያዝ ችግሮች ላይ ለበርካታ ዓመታት ጥናት የሰሩት እና መጽሃፍ የጻፉት ሃብቴ ጀቤሳ (ዶ/ር) ሰዎችን አለመስማት፣ ለሰዎች ቅን መሆን አለመቻል፣ በስራ እና በትምህርት ውጤታማ አለመሆን የመቀንጨር ችግር ካለባቸው ሰዎች ጥቂቶቹ ምልክቶች እንደሆኑ ያስረዳሉ፡፡


መቀንጭር በስርዓተ ምግብ አለመስተካካል ምክንያት እንደሚከሰት የሚያስረዱት ሀብቴ ጀቤሳ(ዶ/ር) ችግሩን ለመቀነስ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም በሚፈለገው ደረጃ ችግሩ አለመቀነሱን አስረድተዋል፡፡


በሀገሪቱ ቁመታቸው እና አዕምሯቸው ከእድሚያቸው እኩል የማያድጉ ወይም የመቀንጭር ችግር ያለባቸው 37 ከመቶ ህጻናት እንደሚወለዱ ባለሞያው ጥቁመዋል፡፡


በኢትዮጵያ የመቀንጨርን ችግር እንደ በሽታ አለመቆጠሩ ጉዳዩ ትኩረት እንዳያገኝ ማድረጉን የሚናገሩት ባለሞያው ይህም በሀገር ልማት ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ እንዳለ ነግረውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..

ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page