top of page

መስከረም 26 2018 - ''ግጭቶችን ለመፍታት መንግስት ከሀይል ይልቅ የእርቅና የሰላም አማራጭ መንገድን መከታተሉን ይቀጥላል'' ፕሬዘዳንት ታዬ አፅቀስላሴ

  • sheger1021fm
  • Oct 6
  • 1 min read

በየአካባቢው የሚታዩ ግጭቶችን ለመፍታት መንግስት ከሀይል ይልቅ የእርቅና የሰላም አማራጭ መንገድን መከታተሉን ይቀጥላል ተባለ፡፡


ፕሬዘዳንት ታዬ አፅቀስላሴ የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የ2018 ዓ.ም የስራ ዘመን የመክፈቻ ንግግርን አድርገዋል፡፡


በመክፈቻ ንግግራቸው በተለያዩ ዘርፎች በየአመቱ ትኩረት የሚደረግባቸውን ጉዳዮች ዘርዝረዋል፡፡

ree

ሰላምን በተመለከተም ሲያነሱ በየአካባቢው የሚታዩ ግጭቶችን በሀይል ማረቅና ማስተካከል ይቻላል ብለዋል፡፡


በየጊዜው የሚታዩ የሀይል እንቅስቃሴዎችን ለማስቆም የሚያስችል ሙሉ ዝግጁነት እና ዘመናዊ አቅም መንግስት አለው ብለዋል፡፡


የዛሬውን ግጭት በሀይል በማሸነፍ ለመጪው ትውልድ ቂም እና ቁርሾን ላለማስተላለፍ ሲባል ግን መንግስት አሁንም የእርቅና የሰላም አማራጭን ምርጫው ያደርጋል ብለዋል ፕሬዘዳንቱ በንግግራቸው፡፡


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page