top of page

መስከረም 24፣2017 - በአረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያዊያን አድራሻቸው በአግባቡ ተመዝግቦ እና መብታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ያግዛል የተባለለት ስምምነት ተፈረመ

  • sheger1021fm
  • Oct 4, 2024
  • 1 min read

ስምምነት የተደረገውም በኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን እና በኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን በኩል ነው።


ስምምነቱም ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ለመሄድ ህገ-ወጥ የውጭ ሀገራት ጉዞን ለማስቀረትና በህጋዊ መንገድ የሚሄዱ ዜጎችን መረጃ ለማወቅ የሚያግዝ፣ መብት እና ደህንነታቸውንም የሚያስጠበቅ ነው ተብሏል።


ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በአሰሪዎቻቸው የሚደርስባቸው እንግልት እና እስራት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑም ተነግሯል።


የዚህም ዋነኛው ምክንያት ደግሞ ሰዎች በህገወጥ መንገድ በተሰማሩ የውጪ ሀገር ስራ ስምሪት ኤጀንሲዎች አማካኝነት በህገ-ወጥ መንገድ ስለሚሄዱ ነው ተብሏል።


በዚህም በህገ-ወጥ መንገድ የወጡ ዜጎች በቂ መረጃ ስለሌለ እና አድራሻቸውም ስለማይታወቅ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ እንቅፋት ስለመሆኑም ተነግሯል፡፡




ፍቅሩ አምባቸው

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page