top of page

መስከረም 24፣2016 - የቴሌኮም ማጭበርበር ሲፈፅሙ የተደረሰባቸው ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Oct 6, 2023
  • 1 min read

የቴሌኮም ማጭበርበር ሲፈፅሙ የተደረሰባቸው 30 ተጠርጣሪ ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ።


ከ73 በላይ የቴሌኮም ማጭበርበሪያ መሳሪያዎችም ተይዘዋል ተብሏል።


ግለሰቦቹ በቁጥር ስር የዋሉት በአዲስ አበባ፣ ሸገር ከተማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ አዳማ፣ ሐዋሳ እና ጅማ ከተሞች መሆኑ ተነግሯል።


ግለሰቦቹ እና የተሌኮም ማጭበርበሪያ መሳሪያዎቹ ሊያዙ የቻሉት የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር፣ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እና ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጋር በመተበበር እንዲሁም ከቴሌኮም አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ባለሙያዎችና ከማኅበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ለሶስት ወራት በሰሩት ስራ መሆንን ሰምተናል።

ተጠርጣሪዎቹ የተለያዩ የግለሠብ ቤቶችንና ግቢዎችን በመከራየት ሲያጭበርብሩ ቆይተዋል የተባለ ሲሆን ለዚህም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ከ200 ሺ በላይ የሳፋሪኮም እና ኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዶች መያዛቸውን ተነግሯል ፡፡


በቁጥጥር ስር ከዋሉ የማጭበርበሪያ ጌትዌይ መካከልም በአንድ ጊዜ 127 ሲም ካርድ መያዝ የሚችል መሣሪያ መገኘቱንም ተጠቁሟል፡፡


የሚፈጸመው የማጭበርበር ድርጊቶች ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማግኘት የሚገባትን የውጭ ምንዛሪ አስቀርቷል፤ ኢትዮ ቴሌኮም ብቻ ባለፉት ስድስት ወራት ከ500 ሚልዮን ብር በላይ ብር አሳጥቷል ተብሏል፡፡


መሣሪያዎቹ በሕገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ናቸው የተባለ ሲሆን፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ይሁን ከሳፋሪኮም ምንም እውቅና የሌላቸው ነገር ግን ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን ኢትዮ ቴሌኮም ወይም ሳፋሪኮም በዘረጋው ኔትወርክ ሳይሆን ራሳቸው በዘረጉት የማጭበርበሪያ ጌትዌይ ለደንበኞች የሚያቀርቡ ነበሩ ተብሏል ፡፡

የማጭበርበሪያ መሣሪያዎቹ ከጎረቤት ሀገራት በድንበር በኩል እስከ መሀል ከተማ ድረስ የሚቀባበሉ ደላሎች፣ በርካታ የኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም ሲም ካርድ እና ሞባይል ካርድ ለእነዚህ አጭበርባሪዎች የሚያደርሱ ተባባሪ ወንጀለኞች እንደሚገኙበት ተጠቅሷል፡፡


ተጠርጣሪዎች መቀመጫቸውን ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ሌሎች ሀገራት ካደረጉ ዜጎች ጋር በመመሳጠር እና ተቀጥረው በመሥራት ተሳትፎ ሲያደርጉ እንደተደረሰባቸው ተጠቁሟል።

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page