top of page

መስከረም 24፣2016 በዲጂታል ኢኮኖሚ ስራ ፈጣራ ላይ ያተኮረ እንቆጷየተሰኘ ጉባኤ ሊካሄድ ነው ተባለ


ጉባኤው ጥቅምት 1 እና 2 በሚሊንየም አዳራሽ ይካሄዳል ነው የተባለው።


የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር ሚንስትር ድኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፉ ላይ ትልቅ አቅም አላት ብለዋል።


እንቆጷ ጉባኤ ሲካሄድ ይህ አቅም በመጠቀም በሀገሪቱ የሥራ እድል መፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።


ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ እንቆጷ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ንቅናቄ ለማስጀመርና ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን አቅም ለሀገር ውስጥና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ማቀዱን አቶ ንጉሱ ተናግረዋል።


የሥራ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ስራ ፈጣሪዎች በዕንቆጷ ጉባኤ ላይ ከባለሀብቶች ጋር እንዲገናኙ እና ሥራዎችን በጋራ የሚሰሩበት እድል የፈጠራል ሲሉ ሚንስትር ድኤታው ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፉ ያላትን አቅም በተመለከተ ከ2014 ጀምሮ ተደጋጋሚ ውይይቶች እየተደረገ ነበር የተባለ ሲሆን ከብሄራዊ የሥራ ጉባኤ ጋር ከ2 አመት በፊት ይህ ጉባኤ ተደርጎ ነበር ተብሏል።


በ2 ቀናት የእንቆጷ ጉባኤ ላይ የፓናል ውይይቶች ፣ ኤግዚቢሽን እና የሥራ ፈጣሪዎች እና ባለሀብቶች ትስስር እንዲያደርጉ ይደረጋል ተብሏል።


ለዲጂታል ዘርፉ ቅልጥፍና የመሰረተ ልማት ስራ ሟሟላት እና የማስተካከል ስራ የስራ እና ክህሎት ሚንስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ተነግሯል።


በጉባኤው ላይ የዘርፉ ምሁራን፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ አህጉራዊ ተቋማት እና አለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ይሳተፋሉ ተብሏል።



በረከት አካሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page