top of page

መስከረም 24፣2016 በዲጂታል ኢኮኖሚ ስራ ፈጣራ ላይ ያተኮረ እንቆጷየተሰኘ ጉባኤ ሊካሄድ ነው ተባለ

  • Oct 5, 2023
  • 1 min read

ጉባኤው ጥቅምት 1 እና 2 በሚሊንየም አዳራሽ ይካሄዳል ነው የተባለው።


የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር ሚንስትር ድኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፉ ላይ ትልቅ አቅም አላት ብለዋል።


እንቆጷ ጉባኤ ሲካሄድ ይህ አቅም በመጠቀም በሀገሪቱ የሥራ እድል መፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።


ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ እንቆጷ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ንቅናቄ ለማስጀመርና ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን አቅም ለሀገር ውስጥና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ማቀዱን አቶ ንጉሱ ተናግረዋል።


የሥራ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ስራ ፈጣሪዎች በዕንቆጷ ጉባኤ ላይ ከባለሀብቶች ጋር እንዲገናኙ እና ሥራዎችን በጋራ የሚሰሩበት እድል የፈጠራል ሲሉ ሚንስትር ድኤታው ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፉ ያላትን አቅም በተመለከተ ከ2014 ጀምሮ ተደጋጋሚ ውይይቶች እየተደረገ ነበር የተባለ ሲሆን ከብሄራዊ የሥራ ጉባኤ ጋር ከ2 አመት በፊት ይህ ጉባኤ ተደርጎ ነበር ተብሏል።


በ2 ቀናት የእንቆጷ ጉባኤ ላይ የፓናል ውይይቶች ፣ ኤግዚቢሽን እና የሥራ ፈጣሪዎች እና ባለሀብቶች ትስስር እንዲያደርጉ ይደረጋል ተብሏል።


ለዲጂታል ዘርፉ ቅልጥፍና የመሰረተ ልማት ስራ ሟሟላት እና የማስተካከል ስራ የስራ እና ክህሎት ሚንስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ተነግሯል።


በጉባኤው ላይ የዘርፉ ምሁራን፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ አህጉራዊ ተቋማት እና አለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ይሳተፋሉ ተብሏል።



በረከት አካሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page