top of page

መስከረም 23፣2017 - በተለያየ የአለም ሀገራት የሚኖሩ እና የሌላ ሀገር ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ቀዳሚ ጥያቄያቸው ከኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት ማግኘት ነው ተባለ

በተለያየ የአለም ሀገራት የሚኖሩ እና የሌላ ሀገር ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ቀዳሚ ጥያቄያቸው ከኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት ማግኘት ነው ተባለ፡፡


ይህን ያለው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር ነው፡፡


በተለያየ የአለም ክፍል የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጥምር ዜግነት በኢትዮጵያ እንዲፈቀድ ጥያቄ ማቅረባቸውን የዲያስፖራ ማህበር ተናግሯል፡፡


ዲያስፖራው በሀገሩ ጉዳይ የመምረጥ፣ የመመረጥ መብት እንዲኖረው ይፈልጋል ሲሉ የነገሩን የማህበሩ ምክትል ፕሬዘዳንት ደመቀ ነጋሣ፤ ለዚህም ኢትዮጵያ የጥምር ዜግነት እንድትፍቅድ በማህበሩ በኩል ለመንግስት ጥያቄ ቀርቧል ብለውናል፡፡


በሌላ በኩል በመላው አለም የሚገኙ የሀገር ልጆች በሃገራቸው ጉዳይ ያገበኛል ብለው እውቀታቸው፣ ጉልበታቸው ገንዘባቸው ለሀገራቸው እንዲያደርጉ ያግዛል የተባለ የዲያስፖራ ሳምንት መዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡

የዲያስፖራ ሳምንቱ በገና በዓል ሰሞን በአዲስ አበባ፣ በካናዳ ቶሮንቶ ኤግዚብሽን ሲንፖዚየም፣ የእራት ግብዣ እንዲሁም ታላቅ የዲያስፖራ ሩጫ ያካተተ መሆኑን የማህበሩ ምክትል ፕሬዘዳንት ነግረውናል፡፡


በእነዚህ ዝግጅቶች ዲያስፖራዉ በሀገሩ እንዲሰራ የፖሊሲና የአሰራር ማነቆዎች የተሻለ መፍትሔ እንዲኖር ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በቅርበት መስራት፣ ዲያስፖራዉ ለሚፈልገው የኢንቨስትመንትና መሰል ጉዳዮች ድጋፍ ሲያስፈልገው ተገቢዉን ድጋፍ መስጠት፣ ለሀገሩ ጉዳይ ጉልህ ተሳትፎ እንዲኖረው ማስቻልና የመሳሰሉት ቁልፍ ጉዳዮች ይሰራባቸዋል ተብሏል፡፡


በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵዊያን በሀገራቸው መጥተው ገንዘባቸው፣ እውቀታቸው ስራ ላይ እንዲውል በተደጋጋሚ ጥሪ ሲቀርብላቸው ይሰማል፡፡


በሌላ በኩል ግን የሀገሪቱ ቢውሮክራሲ፣ ተገማች ያልሆነ የህጎች መለዋወጥ እና የፀጥታ ችግር በዲያስፖራው በኩል ይነሳል፡፡


የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር እነዚህ ችግሮች እንዲፈቱ ምን ሰራ ምንስ የተለወጠ ነገር አለ ያልናቸው አቶ ደመቀ ነጋሣ ብዙ ነገር ተለውጧል ይላሉ፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page