መስከረም 22 2018 - በደብረ ብርሃን የተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች 23,000 ተፈናቀዮች ይገኛሉ፡፡
- sheger1021fm
- Oct 2, 2025
- 1 min read
በደብረ ብርሃን የተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች 23,000 ተፈናቀዮች ይገኛሉ፡፡
ተፈናቃዮች የሚቀርብላቸው ድጋፍ መሻሻል አለማሳየቱን ተናግረዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸው መልስ ለመስጠት አልፈቀዱም፡፡
ተፈናቃዮች በየመጠለያ ጣቢያው ተጠልለው መኖር ከጀመሩ ከ4 ዓመት በላይ ሆኗቸዋል፡፡
ተፈናቃዮቹ በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ በነበሩባቸው 4 ዓመታት የሚደረግላቸው ድጋፍ ወቅቱን እየጠበቀ እንደማይመጣላቸው በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በተለይም ደግሞ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ረጂ ተቋማት እንዲወጡ መደረጉን ተከትሎ ችግሩ ከአቅም በላይ እንደሆነባቸው ነግረውናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx











Comments