የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ የ2017 የትምህርት ዘመን በቅድመ ምረቃ 5,300 ተማሪዎችን እንደሚቀበል ተናገረ፡፡
ይህን አስመልክቶ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ዩኒቨርሲቲው #ራስ_ገዝ መሆኑን ተከትሎ በዘንድሮ ዓመት የሚቀበላቸው ተማሪዎችን መልምሎና ፈትኖ ማዘጋጀቱን የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ጄሉ ኡመር(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ከሚቀበላቸው #ተማሪዎች መካከል 2,660ዎቹ በመንግስት ወጪያቸው የሚሸፈን ሲሆን የተቀሩት 2,640ዎቹ በግላቸው ከፍለው የሚማሩ ናቸው፡፡
ተማሪዎቹ የሚከፍሉት የገንዘብ መጠን እንደሚወስዱት ኮርስ የሚለያይ ሆኖ በኮርስ ከ600 ብር እስከ 2000 ብር የሚደርስ መሆኑንም ዶ/ር ጄሉ አስረድተዋል፡፡
በአጠቃላይ ከሚቀበላቸው ተማሪዎች 52 በመቶዎቹ ወንዶች ሲሆኑ 48 በመቶዎቹ ሴቶች ናቸው ተብሏል፡፡
Comments