top of page

መስከረም 22፣2017 - አ.አ.ዩ የ2017 የት/ት ዘመን በቅድመ ምረቃ 5,300 ተማሪዎችን እንደሚቀበል ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 2, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ የ2017 የትምህርት ዘመን በቅድመ ምረቃ 5,300 ተማሪዎችን እንደሚቀበል ተናገረ፡፡


ይህን አስመልክቶ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ዩኒቨርሲቲው #ራስ_ገዝ መሆኑን ተከትሎ በዘንድሮ ዓመት የሚቀበላቸው ተማሪዎችን መልምሎና ፈትኖ ማዘጋጀቱን የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ጄሉ ኡመር(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ከሚቀበላቸው #ተማሪዎች መካከል 2,660ዎቹ በመንግስት ወጪያቸው የሚሸፈን ሲሆን የተቀሩት 2,640ዎቹ በግላቸው ከፍለው የሚማሩ ናቸው፡፡


ተማሪዎቹ የሚከፍሉት የገንዘብ መጠን እንደሚወስዱት ኮርስ የሚለያይ ሆኖ በኮርስ ከ600 ብር እስከ 2000 ብር የሚደርስ መሆኑንም ዶ/ር ጄሉ አስረድተዋል፡፡


በአጠቃላይ ከሚቀበላቸው ተማሪዎች 52 በመቶዎቹ ወንዶች ሲሆኑ 48 በመቶዎቹ ሴቶች ናቸው ተብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page