top of page

መስከረም 21፣2017 - የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ውጤት ለመቁጠር የህግ ክፍተቶችንና አሰራሩን እያጠባበቀ መሆኑን ተናግሯል

የኢትዮዽያን ገቢ እና ወጪ ንግድ በከፍተኛ ደረጃ ጉልበት እንዲሆነው የተነጠፈው የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ውጤት ለመቁጠር የህግ ክፍተቶችንና አሰራሩን እያጠባበቀ መሆኑን ተናግሯል።


አክስዮን ማህበሩ ከህግ ማዕቀፍ ውጪ እስካሁን ለካሳ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ከፍያለሁ ብሏል።


የቁም ከብቱን፣ ማዳበሪያውን፣ ፍራፍሬውንና ሌላውንም ጭነት ሀገር ለሀገር እያሳበረ የሚጓዘው ባቡር በልማድና አለም አቀፍ ህጉ እየጣሰበት የሚፈለገው ውጤት እንዳይመጣ ሲፈተን መቆየቱንም ሰምተናል።


በተነጠፈው የባቡር መንገድና ሀዲድ እክል እየገጠሙ ከፍተኛ የሀገሪቱን ገቢና ወጪ እቃዎች አዝለው የሚጓዙ ባቡሮች በሰው ባህሪና ሰው ሰራሽ ተፈጥሮ ምክንያት እየታገተ የሐገር ሐብት ሲባክን ቆይቷል ተብሏል።


ይህ ባህሪና ጠባይ አለምአቀፍ ህግና ደንብ የሚጥስ እንዲሁም ለባቡር አጠቃላይ ጭነት ስራና ትራንስፖርት ፈተና መሆኑን አክስዮን ማህበሩ ለሸገር 102.1 ራዲዮ ነግሯል።


የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የሀገሪቱ ገቢና ወጪ ንግድ እንዲበረታ ከፍተኛ አደራ የተጣለበት መሆኑን በመረዳት ከህግና ህግ ነክ ጉዳዮች ጋር ያሉትን ክፍተቶች በማጠባበቅ፣ ከሚመለከታቸውም ጋር በህብረት ለመስራት ወገቡን እንደታጠቀም ሰምተናል።


ተህቦ ንጉሴ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page