top of page

መስከረም 2፣2017 - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥቅምት 5 ጀምሮ ወደ ፖርት ሱዳን በረራ እጀምራለሁ አለ

  • Sep 12, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፊታችን ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ዕለታዊ በረራ እንደሚጀምር ተናግሯል፡፡


ወደ ፖርት ሱዳን በረራ መጀመሩ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሀገራት ያላትን የመዳረሻ ቁጥር ያሳድጋል፤ የንግድና ቱሪዝም ትስስርን በማጎልበት የቀጣናውን የኢኮኖሚ እድገት ያቀለጥፈዋል ብሏል የአየር መንገዱ፡፡

በተያያዘም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኬኒያ ናይሮቢ የሚገኘው የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሠራተኞች በስራ ማቆም አድማ ላይ በመሆናቸው ምክንያት፤ ወደ ናይሮቢ የሚያደርገው በረራ መቋረጡን ጠቅሷል፡፡


ወደ ናይሮቢ የማደርገው በረራ በታቀደለት መርኃ ግብር እየተከናወነ አለመሆኑን እወቁልኝ ብሏል።


አየር መንገዱ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ እንደሚገኝ ገልፆ በክስተቱ ለተፈጠረው መስተጓጎል ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።


ደንበኞች የበለጠ መረጃ ለማግኘት የዓለም አቀፍ የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል ስልክ ቁጥር ወይም በ 6787 በመደወል አልያም ናይሮቢ የሚገኘውን ትኬት ሽያጭ ቢሮ በአካል በመገኘት ማግኘት እንደሚቻል አየር መንገዱ ተናግሯል።

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page