top of page

መስከረም 14፣2017 - በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የጥቃት ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ከሚታሰቡ ቦታዎች ራሳቸውን እንዲያርቁ በቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንፅላ ፅ/ቤት ጠየቀ

  • sheger1021fm
  • Sep 24, 2024
  • 1 min read

በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የጥቃት ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ከሚታሰቡ ቦታዎች ራሳቸውን እንዲያርቁ በቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንፅላ ፅ/ቤት ጠየቀ፡፡


በሊባኖስና በቀጠናው ያለው ወቅታዊ የፀጥታ ስጋት እንዲሁም ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ መጥቷል ያለው ቆንፅላ ፅህፈት ቤቱ በተለይ በደቡባዊ ሊባኖስ እና በቤይሩት አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል ብሏል፡፡

ቆንፅላ ፅህፈት ቤቱ ጉዳዩ አሳሳቢ መሆኑ ተረድቶ የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር እየሰራ እንዳለ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ አስረገድቷል፡፡


ከሊባኖስ መንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችን መተግበር የከፋ ነገር በሚያጋጥምበት ወቅት ደግሞ በቆንፅላው የቀጥታ የስልክ መስመር ዜጎች እንዲደውሉ ፅህፈት ቤቱ ጠይቋል፡፡


ችግሩ እየከፋ የሚሄድ ከሆነ ወደፊት የሚወሰዱ እርምጃዎችን በፌስ ቡክ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ የማሳውቅ ይሆናል ብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Kommentare


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page