top of page

መስከረም 13፣2017 - ኢትዮጵያ ፖሊሲዎች እያሻሻለች መምጣቷን ተከትሎ ቢዝነስ ስራ ኢንቨስትመንት እና ሌላው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከነበረበት ጠባይ ውጪ እየተጓዘ ነው

ኢትዮጵያ የገንዘብ ሥርዓቷን በፍጥነትና በተለዋዋጭ ፖሊሲዎች እያሻሻለች መምጣቷን ተከትሎ ቢዝነስ ስራ ኢንቨስትመንት እና ሌላው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከነበረበት ጠባይ ውጪ እየተጓዘ ነው፡፡


ወትሮም ቢሆን ከውጭ ምንዛሪ ጋር በተገናኘ በይጨምራል ሀሳብና ያልተገመተ የንግድ ጠባይ የጥቁር ገበያው እየገነገነ መጥቶ ቆይቷል።


ይህን የተረዳው ብሔራዊ ባንክ የተለያዩ የገንዘብ ለውጥ ፖሊሲዎችንና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደሮች ላይ ማሻሻያ አድርጓል።


ከዚህ መሀል ብሔራዊ ባንክ ነፃ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ያለማንም የባንክ ግንኙነት በተናጠል ፈቃድ እየሰጠ ነው።


በዚህ ረገድ የብሔራዊ ባንክን መስፈርት አማልቶ ኢትዮ ፎሬክስ የተባለ ድርጅት ነፃ የውጭ ምንዛሪ ቢሮ ለመክፈት ፈቃድ ማግኘቱን ለሸገር ራዲዮ ነግሯል።


የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ በሁለት ቀን ውስጥ ወደ መደበኛ ስራ እንደሚገቡ አስረድተዋል።



ተህቦ ንጉሴ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page