top of page

መስከረም 12 2018 ከዛሬ  ጀምሮ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል ተባለ፡፡           

  • sheger1021fm
  • Sep 22
  • 1 min read

የህዳሴ ግድብ ለመጎብኘት ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ ማድረግ ይቻላል ተብሏል፡፡።            


ለጉብኝት ጉዞ የሚደረገው በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል እንደሆነም ተነግሯል፡፡


ለጉብኝት መሄድ የሚቻለው ከ50 ሰው ጀምሮ እንደሆነም ሰምተናል፡፡

ree

ጉዞ ማድረግ የሚቻለው ደርሶ መልስ እንደሆነም የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ተናግረዋል ፡፡


በዚህም የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጎብኘት የምትፈልጉ  ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ትኬት ቢሮዎች መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡


ከግለሰቦች በተጨማሪም ተቋማት፣ የተለያዩ ጥናት አድራጊዎች፣ ተመራማሪዎች ጉብኝት ማድረግ እንደሚችሉ ሚኒስትሯ አስረድተዋል፡፡


አሁን ላይ የህዳሴ ግድቡን መጎብኘት የሚቻለው በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ብቻ እንደሆነም ተነግሯል፡፡


ለዚሁ ሲባልም በሳምንት ሁለት ቀን በረራ እንደሚኖር  ሰምተናል፡፡


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page