top of page

መስከረም 11፣2017 - ለማህበረሰብ በጎ ሰርተዋል፣ በቢዝነስ ስራ ፈጠራ በስፖርትና ኪነ ጥበብ የተሻለ ፈፅመዋል በሚል መስፈርት በየዓመቱ እጩዎችን የሚያስታውሰው የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ከወዲሁ ስንዱ መሆኑ ተሰምቷል

  • Sep 21, 2024
  • 1 min read

ለማህበረሰብ በጎ ሰርተዋል፣ በቢዝነስ ስራ ፈጠራ በስፖርትና ኪነ ጥበብ የተሻለ ፈፅመዋል በሚል መስፈርት በየዓመቱ እጩዎችን የሚያስታውሰው የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ከወዲሁ ስንዱ መሆኑ ተሰምቷል፡፡


ማህበረሰብን አንፀዋል በሚል ሽልማቱን ለማበርከትም አምስት ሴት የሀገር ሰዎች ተለይተዋል ተብሏል፡፡


ይህንን ወሬ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 የነገሩት የአፍሪካን ኢምፓክት አዋርድና የግራንድ አፍሪካ ራን ማኔጅመንት ዳይሬክተር ጋሻው አብዛ(ዶ/ር) ናቸው፡፡


በዚሁ የማስታወሻ ሽልማት ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ፣ ድምፃዊት አስቴር አወቀ፣ አትሌት ትዕግስት አሰፋ እና አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፉ እርብቃ ሀይሌ ተሸላሚ መሆናቸው አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡


ይህ ዝግጅት በ2024 በአሜሪካ ሜሪላንድ ይካሄዳል፡፡


በእለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ባለስልጣን ሴናተሮች፣ ከንቲባና ሌሎችም ሀላፊዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡


እጩ ተሸላሚዎቹ በእለቱ በመገኘት ማስታወሻቸውንም እንደሚቀበሉ አዘጋጆቹ ነግረውናል፡፡




ተህቦ ንጉሴ

Recent Posts

See All
በ'ፊንቴክ' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ፖሊስ የጠየቀው የተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ላይ ለመወሰን ፍርድ ቤት ለነገ ቀጥሯል።

ከ"ፊንቴክ" (Fintech) ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ በከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ በቀሪ የምርመራ ስራዎች ምክንያት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page