top of page

መስከረም 10፣2017 - በዶሮ መኖ ላይ የቫት ክፍያ በመጨመሩ እና በሌሎችም ምክንያቶች በዘርፉ የተሰማሩ ከገበያ እየወጡ መሆኑ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Sep 20, 2024
  • 1 min read

በዶሮ መኖ ላይ የቫት ክፍያ በመጨመሩ እና በሌሎችም ምክንያቶች በዘርፉ የተሰማሩ አምራቾች ኪሳራ እንደገጠማቸው እና ከገበያም እየወጡ መሆኑ ተነገረ።


በዶሮ መኖ ላይ ቫት መጨመሩ የመኖ እና የማምረቻ ዋጋ መጨመርም በገበያው ላይ የእንቁላል ዋጋም እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል ተብሏል።


የኢትዮጵያ ዶሮ አርቢዎች እና አቀናባባሪዎች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዝናው ፀሐይነህ ከዚህ ቀደም የእንቁላል እና የዶሮ ምርት በገበያ ላይ ከፍተኛ እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ግን በተለይ የዶሮ መኖ ላይ ቫት እንዲኖር ከተወሰነ በኋላ አምራቾች ክፉኛ እንደተፈተኑ ነግረውናል።


የዶሮ መኖ ዋጋ የጨመረበት ምክንያትም ከውጪ የሚገቡ የመኖ የማቀነባበሪያ ግብአቶችን ለማስገባት የዶላር እጥረት ስላለ እንደሆነም ሰምተናል።


ከሀገር ቤት ከሚጠቀሙበት ግብዓት መካከል የሆነው የበቆሎ እጥረትም መኖሩን ሰምተናል።


በሌላ በኩል በተለያዩ አካባቢዎች ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያትም የተመረቱ ምርቶችም ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ለማዳረስ እንደተቸገሩም አቶ ዝናው ነግረውናል።





ፍቅሩ አምባቸው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page