top of page

ሐምሌ 6፣ 2016 - የእርዳታ እህልን ጨምሮ ሊመዘበር የነበረ 2.8 ቢሊዮን ብርን ማዳን መቻሉን የስነ - ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ተናገረ፡፡

  • Jul 13, 2024
  • 1 min read

የእርዳታ እህልን ጨምሮ ሊመዘበር የነበረ 2.8 ቢሊዮን ብርን ማዳን መቻሉን የስነምገባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ተናገረ፡፡

 

ኮሚሽኑ ሊመዘበር የነበረ ከ2.8 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ፣ 8490 የአሜሪካን ዶላር እና ከ46.4 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ የገጠርና የከተነማ መሬት በተጠናቀቀዉ በበጀት ዓመት አድኛለዉ ሲል ለሸገር ነግሯል፡፡

 

በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ገዛኸኝ ጋሻዉ፤ በተሰራ 1087 የአስቸኳይ መከላከል ስራ 2.8 ቢሊዮን ብር፣ 46.467 ሚሊዮን ካሬ ሜትር የመንግስትና የህዝብ ሀብት ከምዝበራ ድኗል ሲሉ ነግረውናል፡፡

የአስቸኳይ ሙስና መከላከል የተሰራባቸዉ ርዕሰ ጉዳይዎችም ግዢ ንብረት ማስውገድ የገጠር እና ከተማ መሬት እንዲሁም የእርዳታ እህል ነዉ ተብሏል፡፡

 

በምዝበራ ሂደትም ከበለሞያ እስከ የስራ ሃላፊዎች ድረስ ተሳትፈዋል ያሉት መሪ ስራ አስፈጻሚዉ ጉዳያቸዉ በህግ ተይዟል ብለዋል፡፡

 

ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page