መንግስት በውጭ እርዳታ እና ብድር ተደግፎ ከሚከውናቸው የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ይገኙበታል፡፡
ይሁንና አንዳንድ ክልሎች ለዚሁ አላማ የሚሰጣቸው ገንዘብ በአግባቡ ሲጠቀሙት፤ ሌሎች ደግሞ እያባከኑት ነው ሲል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
ፕሮጀክቶች ከተሞችን ብቻ ማዕከል ማድረጋቸው ደግሞ ሌላው ችግር ነው ተብሏል፡፡
ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን የተለያዩ አይነት ስራዎችን እየሰሩ እንደሆነ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
Comments