ሐምሌ 5፣ 2016 - አንዳንድ ክልሎች ለመጠጥ ውሃ የሚሰጣቸው ገንዘብ እያባከኑት ነው ተባለ
- sheger1021fm
- Jul 12, 2024
- 1 min read
መንግስት በውጭ እርዳታ እና ብድር ተደግፎ ከሚከውናቸው የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ይገኙበታል፡፡
ይሁንና አንዳንድ ክልሎች ለዚሁ አላማ የሚሰጣቸው ገንዘብ በአግባቡ ሲጠቀሙት፤ ሌሎች ደግሞ እያባከኑት ነው ሲል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
ፕሮጀክቶች ከተሞችን ብቻ ማዕከል ማድረጋቸው ደግሞ ሌላው ችግር ነው ተብሏል፡፡
ከልማት አጋሮች ጋር በመሆን የተለያዩ አይነት ስራዎችን እየሰሩ እንደሆነ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
Comentarios