top of page

ሐምሌ 5፣ 2016 - በኢትዮጵያ በተለያዩ ጉዳቶች የሚፈጠሩ አለመግባባቶች መፍትሄ እንዲያገኙ ወደ ፍርድ ቤቶች ማምራት የተለመደ ነው፡፡

  • sheger1021fm
  • Jul 12, 2024
  • 1 min read

ይህ ደግሞ ፍርድ ቤቶች ላይ ያለውን ጫና እያበረታው መሆኑን ይነገራል፡፡


በመሆኑም ወደ ፍርድ ቤቶች ከመሄድ አስቀድሞ አማራጭ የውዝግብ መፍቻ ዘዴዎችን መጠቀም አስፈላጊ ነው ተብሏል፡፡


‘’አማራጭ የውዝግብ መፍቻ ዘዴዎችን ህብረተሰብ ትስስርን ከመፍጠር አንፃር ያለውን ሚና’’ በሚል ሀሳብ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የምርምር ፎረም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቧል፡፡


አስቀድሞ አማራጭ የውዝግብ መፍቻ ዘዴዎችን እስካሁን ግን እየተሰራበት ያለው በንግዱ ማህበረሰብ ያሉትን አለመግባባቶች ለመፍታት ብቻ እንደሆነ በዝግጅቱ ጥናት ያቀረቡት ሚስጥረ መሃመድ ተናግረዋል፡፡


ይህ አካሄድ በሌሎች ዘርፎች ቢተገበር አሁን ካለንበት ችግር ልንወጣና ውጤታማ ልንሆን እንችላለንም ብለዋል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page