top of page

ሐምሌ 4፣ 2016 የመንገድ መሰረተ ልማቶች ያልደረሰባቸውን እና ትርፍ አምራች አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

  • sheger1021fm
  • Jul 11, 2024
  • 1 min read

የመንገድ መሰረተ ልማቶች ያልደረሰባቸውን እና ትርፍ አምራች አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡

 

ፕሮጀክቱ በ5 ዓመት ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናልም ተብሏል፡፡

 

ይህ የተባለው ዛሬ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በሰጡት መግለጫቸው ነው፡፡

 

የገጠር መንገድ መሰረተ ልማት ስራ ለ12 ክልሎችና ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጭምር ያካተተ መሆኑን ሰምተናል፡፡

 

ፕሮጀክቱን ለመከወን ወደ 300 ሚሊዮን ዶላር ከአለም ባንክ እርዳታ የተገኘ ሲሆን 107 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ከክልል መንግስታት በጀት የተውጣጣ ነው ተብሏል፡፡

 

በዚህም በድምሩ 407 ሚሊዮን ዶላር ለፕሮጀክቱ በጀት ተይዟል፡፡

ፕሮጀክቱ 126 ወረዳዎችን የሚያዳርስ ሲሆን 7554 ኪሎ ሜትር አዲስ መንገድ ግንባታ ፣ 10071 ኪሎ ሜትር የወረዳ መንገዶች ጥገና፣ 373 ተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያዎች እንዲሁም 715 የቆላማ አካባቢ መሸጋገሪያ ድልድዮች የሚገነቡ መሆኑን ሰምተናል፡፡

 

ፕሮግራሙ ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page