ሐምሌ 30፣2016 - የወለጋ ለ6 ዓመታት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጭ የነበሩ 143 ከተሞችና ቀበሌዎች አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው ተነገረ
- sheger1021fm
- Aug 6, 2024
- 1 min read
በአራቱ የወለጋ ዞኖች ለ6 ዓመታት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጭ የነበሩ 143 ከተሞችና ቀበሌዎች አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው ተነገረ፡፡
በኦሮሚያ ክልል አራቱም የወለጋ ዞኖች 6 ዓመታት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጭ ሆነው የቆዩት በተከሰተው የፀጥታ ችግር ሳቢያ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰ ውድመትና ጉዳት ነው ተብሏል፡፡
በተሰራው የመልሶ ጥገና ስራ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጭ የነበሩ 143 ከተሞችና ቀበሌዎች ዳግም ወደ አገልግሎቱ መመለሳቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናግሯል፡፡

ዳግም አገልግሎት ያገኙት ቦታዎች፤ በምስራቅ ወለጋ ዞን 53 አካባቢዎች፣ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን 36 ቀበሌዎች፣ በምዕራብ ወለጋ ዞን 35 አካባቢዎች እንዲሁም በቄለም ወለጋ ዞን 19 ቀበሌዎች በአጠቃለይ 143 የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞች ናቸው ተብሏል፡፡
በአራቱም ዞኖች የተጎዱና የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መልሶ በመጠገን አገልግሎቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ የሚደረገው ስራም እንደቀጠለም ተቋሙ ጠቅሷል፡፡
ማንያዘዋል ጌታሁን
Comentários