top of page

ሐምሌ 3፣ 2016 - የኢትዮጵያ ስራ ተቋራጮች ማህበር በመንግስት በሚከወኑ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ተቋራጮች በበቂ ሁኔታ እንዲሳተፉ እየተደረጉ አይደለም አለ

  • sheger1021fm
  • Jul 10, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ስራ ተቋራጮች ማህበር በመንግስት በሚከወኑ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ተቋራጮች በበቂ ሁኔታ እንዲሳተፉ እየተደረጉ አይደለም አለ፡፡


በዚህም ምክንያት ‘’የሃገር ውስጥ ተቋራጮች ስራ አጥተዋል’’ ያለ ሲሆን ‘’በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚከወኑ ፕሮጀክቶችም ተሳትፎቸው አነስተኛ ነው’’ ብሏል፡፡


‘’የሀገር ውስጥ ተቋራጮችን መብት ለማስከበር የሚያግዝ ህግ ቢኖርም ህጉ እና መመሪያው እየተተገበረ አይደለም’’ ብሏል ማህበሩ።


የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ግርማ ሀብተማርያም ‘’ከአዲስ አበባ ባለፈ በሀገር ውስጥ የሚከወኑ የልማት ስራዎች የሀገር ውስጥ ተቋራጮች በበቂ ሁኔታ እንዲሳተፉ በህግ ቢቀመጠም ለሀገር ውስጥ ተቋራጮች የሚሰጠው አመለካከት የተዛባ በመሆኑ ህጉ የሚፈቅደልንን መብት እየተከበረልን አይደለም’’ ብለዋል።


የሀገር ዉስጥ ተቋራጮችን ለማበረታታት ህግ ቢወጣም የአተገባበር ክፍተት በመኖሩ አብዛኞቹ ተቋራጮች ስራ እያጡ መሆኑን አቶ ግርማ ነግረውናል።


በዚህም የሀገር ውስጥ ሀብትን የመጠቀም መብታቸው ተነፍጓል ብለዋል።


የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር ያነሳውን ቅሬታ በተመለከተ የሚመለከተውን አካል አነጋግረናል።


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ ቤት ሀላፊ አቶ ሰኚ ክፍሌ በከተማዋ የሚገነቡ ትላልቅም ሆኑ አነስተኛ ፕሮጀክቶች ውስጥ አብዛኛዎቹ ለሃገር ውስጥ ተቋራጭ የተሰጡ ናቸው ይላሉ።


አያይዘውም የሀገር ውስጥ ተቋራጮች ቁጥር እና በፕሮጀክቱ የተሳተፉት ላይመጣጠን ይችላል እሱም ከፕሮጀክቱ ውስንነት አኳያ ነው ሲሉም ነግረውናል።


ፍቅሩ አምባቸው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page