top of page

ሐምሌ 3፣ 2016 የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ፡፡

የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ፡፡


በመኖሪያ መንደር አካባቢ የተገነባውና በሚፈጥረው የአካባቢ ብክለት ነዋሪዎች ሲያማርሩበት የቆየው የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደምም ከቦታው እንዲነሳ በተከማዋ #ፍርድ_ቤት ጉለሌ ምድብ ችሎት ተወስኖበት ነበር፡፡፡


ተከሳሾች የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅ/ቤት እና የኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር ይግባኝ ብለው ሲከራከሩ ቆይተዋል፡፡

የአካባቢውን ህዝብ ወክሎ ቁም ለአካባቢ የተሰኘው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅትም ለአምስት ዓመት በፍርድ ቤት ሞግቶ የመጨረሻ ውሳኔ ከትናንት በስትያ ተሰጥቷል፡፡


ገበያው #የአካባቢ_ብክለት ስለመፍጠር አለመፍጠሩ በገለልተኝነት ማስረጃ እንዲያቀርብ የተጠየቀው የፌዴራሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ብክለት ስለመኖሩ በማረጋገጡ ፍርድ ቤቱ ገበያው ከቦታው እንዲነሳ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን

Comments


bottom of page