top of page

ሐምሌ 27፣2016 - በታገዱ ትምህርት ቤቶች ሲማሩ የነበሩ 29,000 ተማሪዎች ጉዳይ / ‘’በፈረቃ ላስተምር ነው’’ መንግስት

  • sheger1021fm
  • Aug 3, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የግል ትምህርት ቤቶች፤ ከ80 በላይ የሚሆኑት በ2017 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር እንደማይችሉ መነገሩ ይታወሳል።


በመጭው ዓመት የማስተማር ስራውን እንዳይሰሩ #በታገዱ ትምህርት ቤቶችም 29,000 ተማሪዎች ሲማሩ እንደቆዩም ሰምተናል።


ይህን ተከትሎ በ2017 የትምርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበሉ ትምህርት ቤቶች ላይ መጣበብ አይፈጠርም ወይ?

#በአንዳንድ ክፍለ ከተሞችም ይሄው ችግር እያጋጠማቸው እንደሆነ ሀላፊዎች ሲናገሩ ሰምተናል፡፡


የተማሪ ቁጥር መጨመርን ተከትሎም በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ላይ #የፈረቃ_ትምህርት ለመጀመር እንደሚገደዱ ተናግረዋል፡፡


ሸገር ኤፍኤም ራዲዮም፤ ይህንን እና ሌሎች ጥያቄዎችን በመያዝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮን ጠይቋል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page