top of page

ሐምሌ 27፣2016 - በታገዱ ትምህርት ቤቶች ሲማሩ የነበሩ 29,000 ተማሪዎች ጉዳይ / ‘’በፈረቃ ላስተምር ነው’’ መንግስት

በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የግል ትምህርት ቤቶች፤ ከ80 በላይ የሚሆኑት በ2017 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር እንደማይችሉ መነገሩ ይታወሳል።


በመጭው ዓመት የማስተማር ስራውን እንዳይሰሩ #በታገዱ ትምህርት ቤቶችም 29,000 ተማሪዎች ሲማሩ እንደቆዩም ሰምተናል።


ይህን ተከትሎ በ2017 የትምርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበሉ ትምህርት ቤቶች ላይ መጣበብ አይፈጠርም ወይ?

#በአንዳንድ ክፍለ ከተሞችም ይሄው ችግር እያጋጠማቸው እንደሆነ ሀላፊዎች ሲናገሩ ሰምተናል፡፡


የተማሪ ቁጥር መጨመርን ተከትሎም በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ላይ #የፈረቃ_ትምህርት ለመጀመር እንደሚገደዱ ተናግረዋል፡፡


ሸገር ኤፍኤም ራዲዮም፤ ይህንን እና ሌሎች ጥያቄዎችን በመያዝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮን ጠይቋል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ



コメント


bottom of page