በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት /አትሚስ/ በዚያ የወታደሮች ቅናሽ ማድረጌን እቀጥላለሁ አለ፡፡
ለሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት ተልዕኮ ሰራዊት ያዋጡ አገሮች የጦር ሹሞች በቅርቡ በርዕሰ ከተማዋ ሞቃዲሾ በጉዳዩ ላይ እንደተነጋገሩ ዘ ኢስት አፍሪካን ፅፏል፡፡
አዛዦቹ በመጪው መስከረም ወር ተጨማሪ 3 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያስወጡ ተናግረዋል፡፡
አትሚስ ከሰራዊት ቅናሽ በተጨማሪ ደረጃ በደረጃ የጦር ሰፈሮችንም በማስረከብ ላይ ይገኛል፡፡
እስካሁንም 6 የጦር ሰፈሮችን ማስረከቡን ዘገባው አስታውሷል፡፡
አትሚስ ደረጃ በደረጃ ወታደሮቹን እየቀነሰ ቢሆንም በአገሪቱ የአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ስጋትነት ገና እንዳልቀነስ ይነገራል፡፡
የኔነህ ከበደ
![](https://static.wixstatic.com/media/b24dd6_72c7e2e6ea8f42d5b50ef6b6448f2b76~mv2.jpg/v1/fill/w_980,h_653,al_c,q_85,usm_0.66_1.00_0.01,enc_auto/b24dd6_72c7e2e6ea8f42d5b50ef6b6448f2b76~mv2.jpg)
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Yorumlar