top of page

ሐምሌ 27፣2015 - አትሚስ በሶማሊያ የወታደሮች ቅናሽ ማድረጌን እቀጥላለሁ አለ


በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት /አትሚስ/ በዚያ የወታደሮች ቅናሽ ማድረጌን እቀጥላለሁ አለ፡፡


ለሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት ተልዕኮ ሰራዊት ያዋጡ አገሮች የጦር ሹሞች በቅርቡ በርዕሰ ከተማዋ ሞቃዲሾ በጉዳዩ ላይ እንደተነጋገሩ ዘ ኢስት አፍሪካን ፅፏል፡፡


አዛዦቹ በመጪው መስከረም ወር ተጨማሪ 3 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያስወጡ ተናግረዋል፡፡


አትሚስ ከሰራዊት ቅናሽ በተጨማሪ ደረጃ በደረጃ የጦር ሰፈሮችንም በማስረከብ ላይ ይገኛል፡፡


እስካሁንም 6 የጦር ሰፈሮችን ማስረከቡን ዘገባው አስታውሷል፡፡


አትሚስ ደረጃ በደረጃ ወታደሮቹን እየቀነሰ ቢሆንም በአገሪቱ የአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ስጋትነት ገና እንዳልቀነስ ይነገራል፡፡


የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz


Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

Yorumlar


bottom of page