top of page

ሐምሌ 27፣2015 - በኒጀር ኤሌክትሪክ እየጠፋ እና እየተቋረጠ መሆኑ ተሰማ

ወታደራዊ የመንግስት ግልበጣ በተደረገባት ኒጀር ኤሌክትሪክ እየጠፋ እና እየተቋረጠ መሆኑ ተሰማ፡፡


ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ለAFP እንደተናገሩት ችግሩ ያጋጠመው የናይጄሪያው የኤሌክትሪክ ኩባንያ አቅርቦቱን በማቋረጡ ነው፡፡


እንደሚባለው የናይጀሪያው ኩባንያ ወደ ኒጀር የሚያልፈውን ኤሌክትሪክ ከትናንት በስቲያ አንስቶ አቋርጦታል፡፡


ባለፈው እሁድ በናይጀርያዋ መዲና አቡጃ የተሰበሰቡት የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት ምጣኔ ሐብታዊ ማህበር /ኢኮዋስ/ መሪዎች በኒጀር ላይ ማዕቀብ እንደጣሉ ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኤሌክትሪክ መጥፋቱም የማዕቀቡ አካል ሳይሆን አይቀርም ተብሏል፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page