top of page

ሐምሌ 26፣2016 - ‘’ቢ ጂ አይ ኢትዮጵያ’’ ከመደበኛ የማምረት ስራው ጎን ለጎን የተለያዩ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎችን እየከወነ እንደሚገኝ ተናገረ

  • Aug 2, 2024
  • 1 min read

‘’ቢ ጂ አይ ኢትዮጵያ’’ ከመደበኛ የማምረት ስራው ጎን ለጎን የተለያዩ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎችን እየከወነ እንደሚገኝ ተናገረ።


ኩባንያው ፋብሪካዎቼ በሚገኙባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች የጤና እና የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ የራሴን አስተዋጽኦ እያደረጉ ነው ብሏል።


#ዝዋይ በሚገኘው የካስትል ወይን ፋብሪካ አቅራቢያ ለሚኖሩ 500 ሰዎች የጤና መድን ሽፋን መግዛቱን የቢ ጂ አይ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሄርቬ ሚልሃድ ተናግረዋል።


የጤና መድን ሽፋኑ የተገዛላቸው ሰዎች ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው ብለዋል።


በዚያው በዝዋይ አንድ የቅድመ መደበኛ #ትምህርት_ቤት አስገንብቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ማስረከቡን አክለዋል።


የአካባቢው ምህዳር ተጠብቆ እንዲቆይም ሠራተኞቹን እና ማህበረሰቡን በማስተባበር የተለያዩ ችግኞችን እየተከልን ነውም ብለዋል።


በዛሬው ዕለትም ዝዋይ በሚገኘው የካስቴል ወይን ፋብሪካ አቅራቢያ የኩባንያው ሠራተኞች እና የአካባቢው ነዋሪዎች 2000 ችግኞችን ተክለዋል።


ቢጂአይ ኢትዮጵያ የሜታ አቦ ፋብሪካን እና የተለያዩ ፋብሪካዎችን በመግዛት የማምረት አቅማቸውን እያሳደገ እንደሚገኝ ተነግሯል።


ንጋቱ ረጋሳ

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page