ሐምሌ 26፣2016 - በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ያለው የፀጥታ ችግር ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚጓጓዝ ዕርዳታ ላይ ዕክል እየፈጠረ ነው ተባለ
- sheger1021fm
- Aug 2, 2024
- 1 min read
በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ያለው የፀጥታ ችግር ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚጓጓዝ ዕርዳታ ላይ ዕክል እየፈጠረ ነው ተባለ።
የፌዴራል መንግስት ከአዲስ አበባ ለቤንሻኒጉል ጉሙዝ ክልል የሚልከው ዕርዳታ የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎችን አቋርጦ ሲያልፍ በታጣቂዎች ይዘረፋል ተብሏል።
የቤንሻኒጉል ጉሙዝ ክልል በጎረቤት ሡዳን ያለውን ጦርነት በመሸሽ ወደ አካባቢው ለገቡ እንዲሁም በሌሎች ሠው ሰራሽ እና፤ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎች የሚያከፋፍለው ዕርዳታ ከፌዴራል መንግስት እየተላከለት ቢሆንም፤ በአጎራባች ክልሎች ባለ የፀጥታ ችግር ምክንያት ማቅረቡ ፈተና እንደሆነበት ተናግሯል።
የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መሃመድ አብዱላዚዝ እንዳሉት፤ የተላከው ዕርዳታ አቋርጦ በሚያልፍባቸው የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች የሚታየው የፀጥታ ችግር የማጓጓዙን ስራ ፈታኝ አድርጎታል።
ዕርዳታው ሁለቱም ክልሎች ላይ ሲደርስ በታጣቂዎች እንደሚያዝ የተናገሩት ኮሚሽነሩ፤ አንዳንዴም በድርድር፤ ሌላ ጊዜም ደግሞ በፀጥታ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ነው የሚለቀቀው ብለውናል።
Comments