top of page

ሐምሌ 24፣2016b - የአምራቹ የስራ መስክ በሰላም እጦት እና በሌሎችም ምክንያቶች በኢኮኖሚ እድገት እና በስራ እድል ፈጠራ ያሳካል የተባለዉን ግብ እንዳላሳካ ጥናት አሳየ

የአምራቹ የስራ መስክ በሰላም እጦት እና በሌሎችም ምክንያቶች በኢኮኖሚ እድገት እና በስራ እድል ፈጠራ ያሳካል የተባለዉን ግብ እንዳላሳካ ጥናት አሳየ፡፡


ጥናቱን ያስጠናዉ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ በለሞያዎች ማህበር ሲሆን 21ኛው የማህበሩ አለም አቀፍ ኮንፈረስ ላይም ቀርቧል፡፡


ኢትዮጵያ ከግብርና ወደ ኢንደስትሪ መር ልምታደርገዉ የኢኮኖሚ ሽግግር ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የአምራቹ ወይም ማንፋክቸሪንግ ታምኖበት የነበረ ቢሆንም በግጭት እና በተለያዩ ምክንያቶች መስኩ ግቡን ማሳካ አልቻም ተብሏል፡፡


ጥናቱን ያቀረቡት በማህበሩ ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ለሜሳ ታሪኩ(ዶ/ር) የአምራቹ መስክ በኢኮኖሚ እድገት እና በስራ እድል ፈጠራ ለውጥ ያመጣል ተበሎ የነበረ ቢሆንም ያን ማሳካት እንዳልቻለ ነግረውናል፡፡


በዚህም የአምራቹ ዘርፍ በአጠቃላይ እየተፈጠረ ካለው የስራ እድል ድርሻው 5 በመቶ ብቻ እንደሆነ ጥናት አቅራቢው ለሜሳ አስርድተዋል፡፡



Коментарі


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page