top of page

ሐምሌ 24፣2016 - የፍልስጤሙ የጦር ድርጅት ሃማስ የፖለቲካ መሪ ኢስማኤል ሃኒያ ኢራን ውስጥ በአየር ጥቃት መገደላቸው ተነገረ

የፍልስጤሙ የጦር ድርጅት ሃማስ የፖለቲካ መሪ ኢስማኤል ሃኒያ ኢራን ውስጥ በአየር ጥቃት መገደላቸው ተነገረ።


ሃኒያ በኢራን ዋና ከተማ ቴሄራን ባለ መኖሪያ ቤታቸው የተገደሉት በእስራኤል የአየር ጥቃት ነው ሲል ሃማስ ከሷል።


ሃኒያ በቴሄራን የተገኙት በአዲሱ የኢራን ፕሬዝዳንት ማሱድ ኤዝሽኪያን በዓለ ሲመት ላይ ለመታደም እንደነበር ተነግሯል።


አንድ ጠባቂያቸውም አብሮ መገደሉ ታውቋል። ሃማስ ለግድያው እስራኤልን ተጠያቂ አድርጓል።


ኢራን በበኩሏ በግድያው ዙሪያ ማጣራት እያካሃድኩ ነው ብላለች።


እስራኤል ግን ስለ ግድያው እስከ አሁን ያለችው ነገር የለም።

ከዚህ ቀደም ግን ለጥቅምት ሰባቱ ጥቃት በቀል ሃኒያን እና ሌሎች የሃማስ መሪዎችን ለመግደል ስትዝት እንደቆየች አሶሼትድ ፕሬስ አስታውሷል።


ሃማስ ለግድያው እስራኤልን እንደሚበቀል ዝቷል።


የኢራን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይም የሃማሱ መሪ ደም ፈሶ አይቀርም ብሏል።


መቀመጫውን በዌስት ባንክ ያደረገው የፍልስጤም አስተዳደር ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ ደግሞ የሃኒያን ግድያ አውገዘዋል።


ንጋቱ ረጋሳ


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page