top of page

ሐምሌ 24፣2016 - በነዳጅ የሚሰሩ የቤት አውቶሞቢሎች ላይ ተጥሎ የነበረው የውጭ ምንዛሬ ክልከላ አለመነሳቱን የገንዘብ ሚኒስቴር ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Jul 31, 2024
  • 1 min read

በነዳጅ የሚሰሩ የቤት አውቶሞቢሎች ላይ ተጥሎ የነበረው የውጭ ምንዛሬ ክልከላ አለመነሳቱን የገንዘብ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡


በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን መናገሩ ይታወሳል፡፡


"ቅድሚያ የማይሰጣቸው" ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች  ዝርዝር ውስጥ በነዳጅ የሚሰሩ የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢሎች እና ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (የነዳጅ) ይገኙበታል፡፡


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን በሳወቀበት በትላንቱ መግለጫ ተለይተው እግዱ ያልተነሳላቸውን ምርቶች አልጠቀሰም፡፡


የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ በወጣው መግለጫ ደግሞ  በነዳጅ የሚሰሩ ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው የቀረቡ የቤት አውቶሞቢል አና ባለ ሶስት እግር ተሸከርካሪዎች ላይ የተጣለው እገዳ አንደተጠበቀ ነው ብሏል፡፡


ሌሎቹ የውጪ ምንዛሬ ክልከላ ተጥሎባቸው የነበሩ ምርቶች እገዳው መነሳቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ በወጣው ሰርኩላር ላይ ጠቅሷል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page