top of page

ሐምሌ 24፣2015 - ፑቲን ከዩክሬይን ጋር የሚደረግን የሰላም ንግግር አልቃወምም አሉ

  • sheger1021fm
  • Jul 31, 2023
  • 1 min read

የሩሲያውፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬይን ጋር የሚደረግን የሰላም ንግግር አልቃወምም አሉ፡፡


ፑቲንቀደም ሲል በአፍሪካዊያን እና በቻይና የቀረቡ የሰላም ሀሳቦች ለመፍትሄው መልካም መሰረቶች ሆነው አግኝተናቸዋል ማለታቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡


የሩሲያእና የዩክሬይን ጦርነት ከዓመት ከ5 ወራት በላይ ሆኖታል፡፡


ሁለቱምአገሮች አንደራደርም ሲሉ መቆየታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡


ፑቲንከዩክሬይን ጋር ስለ ሰላም መደራደሩን አልቃወምም ስለማለታቸው ከዩክሬይን ሹሞች በኩል የተሰማ አስተያየት የለም፡፡


ሁለቱአገሮች በጦር ግንባሮች ከሚያደርጉት ፍልሚያ በተጨማሪ ወሰን ተሻጋሪ የሚሳኤል እና የሰው አልባ በራሪ አካላት /ድሮኖች/ ጥቃት እየሰነዘሩ መሆኑ ተሰምቷል



የኔነህ ከበደ


የሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page