ሐምሌ 24፣2015 - ፑቲን ከዩክሬይን ጋር የሚደረግን የሰላም ንግግር አልቃወምም አሉ
- sheger1021fm
- Jul 31, 2023
- 1 min read
የሩሲያውፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬይን ጋር የሚደረግን የሰላም ንግግር አልቃወምም አሉ፡፡
ፑቲንቀደም ሲል በአፍሪካዊያን እና በቻይና የቀረቡ የሰላም ሀሳቦች ለመፍትሄው መልካም መሰረቶች ሆነው አግኝተናቸዋል ማለታቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡
የሩሲያእና የዩክሬይን ጦርነት ከዓመት ከ5 ወራት በላይ ሆኖታል፡፡
ሁለቱምአገሮች አንደራደርም ሲሉ መቆየታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ፑቲንከዩክሬይን ጋር ስለ ሰላም መደራደሩን አልቃወምም ስለማለታቸው ከዩክሬይን ሹሞች በኩል የተሰማ አስተያየት የለም፡፡
ሁለቱአገሮች በጦር ግንባሮች ከሚያደርጉት ፍልሚያ በተጨማሪ ወሰን ተሻጋሪ የሚሳኤል እና የሰው አልባ በራሪ አካላት /ድሮኖች/ ጥቃት እየሰነዘሩ መሆኑ ተሰምቷል
የኔነህ ከበደ

የሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
コメント